በራዲዮሎጂካልና ኑክሌር ድንገተኛ አደጋ ዝግጁነትና ምላሽ ላይ ያተኮረ ስልጠና ተሰጠ

የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ባለስልጣን በራዲዮሎጂካልና ኑክሌር ድንገተኛ አደጋ ዝግጁነት ምላሽ አሰጣጥ ላይ ያተኮረ ለተቀዳሚ ምላሽ ሰጭ ባለድርሻ አካላትና ለሚመለከታቸው የባለስልጣኑ ባለሙያዎች ከየካቲት 29/06-04/07/2015 ዓ.ም ድረስ በአዳማ ከተማ ካኔት ሆቴል ስልጠና ሰጠ::

የኡጋንዳ ሪፑብሊክ ፓርላማ አባላት ኦፊሴላዊ የስራ ጉብኝት አደረጉ

የኡጋንዳ ሪፑብሊክ የሳይንስ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ፓርላማ ቋሚ ኮሚቴ አባላት የካቲት 16/2015 ዓ.ም በኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ባለስልጣን መ/ቤት የስራ ጉብኝት አደረጉ፡፡ የቋሚ ኮሚቴ አባላቱ የስራ ጉብኝት ባደረጉበት ወቅት ስለ መስሪያ ቤቱ ታሪካዊ አመጣጥ፣ ዓላማዎች፣ ተልዕኮዎችና አሁናዊ ሁኔታ ዝርዝር ገለጻ የቀረበላቸው ሲሆን ገለጻውን ተከትሎም በዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት ተካሂዷል፡፡ በውይይቱ ወቅት በፓርላማ አባላቱ የተለያዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች የተነሱ ሲሆን ለቀረቡ ጥያቄዎችም እንደየአግባቡ በባለስልጣኑ የስራ ሃላፊዎች መልስና ማብራሪያዎች ተሰጥተዋል፡፡ የፓርላማ ቋሚ ኮሚቴ አባላቱ በነበራቸው የስራ ጉብኝት ብዙ ጠቃሚ መረጃዎችን እንዳገኙ የገለጹ ሲሆን እንደዚህ ዓይነት የልምድ ልውውጥ ፕሮግራሞች ዘርፈ-ብዙ ጥቅሞች ያላቸው ስለመሆኑም አንስተዋል

የባለስልጣኑ ማኔጅመንት አባላት የተተከሉ ችግኞችን ጎበኙ

የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ባለስልጣን ማኔጅመንት አባላት ቀደም ሲል በአረንጓዴ አሻራ ማስቀመጥ ፕሮግራም በሰሜን ሸዋ ልዩ ስሙ መንዲዳ በሚባለው ቦታ በመገኘት በሰራተኞች የተተከሉ ችግኞች የሚገኙበትን ሁኔታ በአካል በመገኘት የጎበኙ ሲሆን ችግኞች በቀጣይ ለሚያስፈልጋቸው የውሃ አቅርቦት የሚያግዝ የውሃ ፓምፕ ሞተርና ሌሎች አስፈላጊ ቁሳቁሶችን ለወረዳ አስተዳደሩ በድጋፍነት አበርክተዋል፡፡ የማኔጅመንት አባላቱ ጉብኝቱን ያካሄዱት ጥር 25/ 2015 ዓ.ም ሲሆን ወደፊት በሚደረጉ የድጋፍና ትብብር ስራዎች ላይም ከወረዳ አስተዳደሩ አመራሮች ጋር ውይይትና የጋራ የመስክ ምልከታ መርሃ ግብር ተከናውኗል፡፡